Thursday 14 January 2016

**ያምላክ ስም አለበት**


ቀድሞ ያሰበውን በልቡ ተመኝቶ፤
ቢሰጠው ፈጣሪ የውስጡን አይቶ፤
የበኩር ልጁን ሚካኤል ሊለው፤
በልቡ፣በውስጡ ቃል-ኪዳን ነበረው፤
ምኞት ተሳካና ኦላም ፈቀደና፤
ወንድ ልጅ ከነ-ቃጭሉ............
ሚካኤል ተባለ ምስጋናንም በስሙ!
የግዕዙ ትርጓሜ በረከት ያዘለ፤
እንደ እግዚአብሔር ያለ፤ማንም የለም ተባለ
....የልብ ሲሞላ ሲሳካም ምኞት፤
ፀሎት ሲሰማ ሲደርስ ከፀባዎት፤
ይቀርብ የለም ወይ ምስጋና በእውነት?፤
የሚካኤል ስሙም ህያው ነው በረከት፤
ያምላክ ስም አለበት።
 
✍✍ #ታታ_አፍሮ +Tata Afro 

‹‹....በመጀመሪያ ወንድ ልጅን ከወልድኩ ሚካኤል ነው የምለው......›› +Teddy Afro 
 
 
 
 
 


አምለሰት ሙጬ

Monday 4 January 2016

"ከእንጨት ፎቁ በላይ ሲመሽ እንገናኝ?"

Addis Abeba First Building. Built 1898.... Ethiopia 


"ቴዲ ልጅ ነው ብላቴና

ስለ ፍቅር መች ያውቅና

አስጠናችው ልቡን ወስዳ

የፍቅር አቦጊዳ"........



የመድረኩ ንጉስ!!

Teddy አንበሳው!!

Abogida n Rass Band


ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ

"ባገሬ ቅኝት የብሔር ቋንቋ
እደሰታለው እኔ አላዝንም በቃ::"


የፍቅር ተጓዥ....


የአጼ ምኒልክ ዘመናዊ ጥበብን መውደድና ወደ ሀገራቸው ለማስገባት የሚያረጉትን ጥረት በእንግሊዝ ሀገር ሆኖ ይሰማ የነበረው /Bentley/ ቤንትሌይ ምኒልክ ታሪኩን ሰምተው ለማየት እጅግ የጓጉለትን መኪና ለምን አልወስድላቸውም ብሎ ተነሳ: ሃሳቡንም "ዌል ሲልይ ቱል ኤንድ ሞተር ማኒፋክቸሪን" /well sell toll and motors manufacturers/ ለተባለ ድርጅት አቅርቦ ከድርጅቱ ጠንካራ መኪናን አገኘ ከዚህም በኋላ /Bentley/ ቤንትሌይ ከጓደኛው ዌልስ ጋር በመሆን መኪናዋን ይዘው ጉዞ ወደ ኢትዮዽያ ጀመሩ ከ27 ቀን የባህር ጉዞ በኋላ ጅቡቲ ደረሱ ከጅቡቲም ድሬደዋ ገቡ: በድሬደዋና በሐረርም ጥቂት ቀናትን ቆይተው ከዚያ ጉዞዋቸውን ወደ አዲስ አበባ አደረጉ: አሸዋማ ቦታዎች ላይ ሰዎች ድንጋይ እያነጠፉ መንገዷን እያቀኑ: አንዳንዴም በበቅሎ እየተጐተተች: ድንጋያማ ቦታና ወንዝ ሲያጋጥም ደግሞ በሰው ሸክም እየተሻገረች: ተራራ ሲሆን እየተገፋች ታኀሳስ 20 ቀን 1900 ዓ/ም የመጀመሪያዋ መኪና አዲስ አበባ ደረሰች: ታኅሳስ 22 ቀን 1900ዓ/ም አጼ ምኒልክ ከእንግሊዝ ሀገር የመጣችሁን መኪና ሊመለከቱ ወጡ መኪናዋን ይዟት የመጣው /Bentley/ ቤንትሌይም የሚገባውን ገለፃ ሰጠ ምኒልክም እየተዟዟሩ ዝቅ ከፍ እያሉ መኪናዋን በሚገባ ተመልክተው ፍጥነቷንም ለማወቅ «አየህ /Bentley/ ቤንትሌይ እኛ በበቅሎ ከዚህ ገበያ ደርሶ መልስ ግማሽ ሰዓት ይበቃናል የመኪናዋን ፍጥነት ማወቅ እንድችል ገበያው ዳር የሚሸጥ አትክልት አለና ሄደህ በመኪናህ እሱን ይዘህ ና?» አሉት: ፈረንጅ ተንኮለኛ ነውና እንዳያሞኙኝም ብለው አብረው ሁለት መኳንንቶቻቸውን ላኩ ቤንትሌይም ከነመኳንንቱ የተላከው ቦታ በፍጥነት ደርሶ መጣ ምኒልክም ሰዓታቸውን አይተው «ጥሩ ነው 6 ደቂቃ ሆናችሁ» አሉ: ከዚያም ምኒልክ መኪናዋ ላይ ወጥተው ከነጂው ጐን ተቀመጡ መኪናዋም ከቀስታ ፍጥነት ተጀምሮ እስከ መጨረሻ ፍጥነት ድረስ እየተነዳች የአዲስ ዓለምን መንገድ አስር ማይል ሄደው ተመለሱ: ከዚህም ቀን በኋላ አጼ ምኒልክ መኪናዋን መንዳት ተለማምደው ለፈተና ቀርበው ሁለት ሰዓት ሙሉ በሚገባ በመንዳት ችሎታቸውን አሳዩ:: ሄልም በመጽሐፉ ''ፐርፌክት ድራይቨር'' /Perfect Driver/ ብሏቸዋል ::በምስሉ ላይ የምንመለከታት መኪናም በምኒልክ ዘመን ከገቡ አምስት መኪናዎች መካከል አንዷ ስትሆን በአሁኑ ሰዓት በብሔራዊ ሙዚየም ግቢ ውስጥ ትገኛለች:: ይች መኪና ዘንድሮ 108 ዓም ሞላት! መኪናዋ ወደ ሃገር ስትገባም በግራና በቀኝ የኢትዮዽያ እና የእንግሊዝን ባንዲራ አንጠልጥለውባት ነበር::

ትልቅ ራዕይ የነበራቸው የቀደሙት አባቶቻችንን እናከበራለን እናፈቅራለን::












ያስተሰርያል