Saturday 5 December 2015

**ባልደራሱ**  Teddy Afro


ከቀን ባራተኛው በዕለተ ሐሙስ 
ከወንድሜጋር ስንጋልብ ፈረስ 
አልያዘውም ኖሮ ልጓሙን አጥብቆ 
አለፈች ህይወቱ ከፈረስ ላይ ወድቆ 
እየጠበቀችን እምዬ ከቤት 
እንዴት ላረዳት ነው የወንድሜን ሞት 
ባልደራሱ........ አልተገራም ወይ ፈረሱ/X2 
ባ....ልደራሱ 
 ምንብዬ ልንገራትX4 
ምንብዬ? 
ምንብዬ ልንገራትX4 
ለምዬ ምንብዬ 
ልንገራትX4 
ምንብዬ? 
ምንብዬ ልንገራትX4 
ለምዬ! 
ባ........ ባልደራሱ? አልተገራም ወይ ፈረሱ 
አልተገራም ወይ ወይ.....? 
አልተገራም ወይ ወይ.....? 
አንተ ባልደራስ የፈረስ አባት 
ነፍሱን ከገነት ለማታስገባት 
ወይኔ ወይኔ 
ለናቴ ልጅ ወይኔ! ወይኔ! 
ከሜዳው ነው ወይ ወይ ከፈረሱ 
ለሞት ያበቃው ምንድነው እሱ? 
ወይኔ ወይኔ 
ለናቴ ልጅ ወይኔ! ወይኔ! 
ሳታበጃጀው ሉጋም ግላሱን 
አንድ የናቴን ልጅ ነሳኸው ነፍሱን 
ወይኔ ወይኔ 
ለናቴ ልጅ ወይኔ! ወይኔ!

No comments:

Post a Comment